1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኮሮና ተሐዋሲ ስርጭት በኦሮሚያ ክልል

ዓርብ፣ መጋቢት 10 2013

በኦሮሚ ክልል መጠኑ ከፍ ያለው የኮሮና ተሐዋሲ ስርጭት ከፍተኛ ስጋት መደቀኑን የክልሉ ጤና ጽ/ቤት ዐስታወቀ። የጽ/ቤቱ የኅብረተሰብ ጤና ድንገተኛ ቁጥጥር ዘርፍ ኃላፊ ለዶይቼ ቬለ እንደገለጹት፤ የቅርብ አሃዞች የሚያመለክቱት የኮሮና ተሐዋሲ ስርጭት ብቻ ሳይሆን በተሐዋሲው የተነሳሱ ሕይወታቸውን የሚያጡ ሰዎችም ቊጥር እየጨመረ ነው።

https://p.dw.com/p/3qsbv
Karte Sodo Ethiopia ENG

ቊጥሩ ከፍ እያለ ነው

በኦሮሚ ክልል መጠኑ ከፍ ማለት የጀመረው የኮሮና ተሐዋሲ ስርጭት ከፍተኛ ስጋት መደቀኑን የክልሉ ጤና ጽ/ቤት ዐስታወቀ። በጤና ጽ/ቤቱ የኅብረተሰብ ጤና ድንገተኛ ቁጥጥር ዘርፍ ኃላፊ ለዶይቼ ቬለ (DW) እንደገለጹት፤ የቅርብ አሃዞች የሚያመለክቱት የኮሮና ተሐዋሲ ስርጭት ብቻ ሳይሆን በተሐዋሲው የተነሳሱ ሕይወታቸውን የሚያጡ ሰዎችም ቊጥር እየጨመረ ነው። በተለይም ባለፉት ሰባት ቀናት በክልሉ በየቀኑ የሚመዘገበው የበሽታው የስርጭት መጠን ከግማሽ በመቶ ከፍ ማለቱን የክልሉ ጤና ጽ/ቤት አክሎ አብራርቷል። ሥዩም ጌቱ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ሥዩም ጌቱ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
እሸቴ በቀለ