የኦሮሚያ የሰዓት እላፊ ገደብ ማሻሻያ
ሐሙስ፣ ኅዳር 9 2014ማስታወቂያ
የኦሮሚያ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ በሰው እና በተሸከርካሪዎች ላይ ጥሎት የነበረዉን የሰዓት ዕላፊ ገደብ አነሳ። የክልሉ መንግሥት ሕገወጥ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር በሚል በጣለዉ የሰዓት እላፊ ገደብ መሰረት፣ ሰዎች መንቀሳቀስ የሚችሉት ከማለዳዉ 11ሰዓት ተኩል እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት፣ መኪኖች ደግሞ ከማለዳዉ 11ሰዓት ተኩል እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት ብቻ ነበር። የክልሉ አቃቤ ሕግ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ግን ገደቡ መሻሻሉን አስታዉቋል።
ስዩም ጌቱ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ