1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሲዳማ ክስተትን ተከትሎ የኢዜማ መግለጫ 

ረቡዕ፣ ሐምሌ 17 2011

መንግሥት በአጥፊዎቹ ላይ "ጠንካራ ርምጃ" እንዲወስድ እንዲሁም ሰላማዊ ዜጎችን ከጥቃት እንዲከላከል ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ /ኢዜማ/ ጠየቀ። ፓርቲዉ በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን የጠፋዉን ሕይወትና የወደመዉን ንብረት ተከትሎ ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ "ኢመደበኛ" ባላቸዉ ኃይላት ላይ ጠንካራ ርምጃ እንዲወሰድ ጠይቆአል።

https://p.dw.com/p/3MbIt
Äthiopien | Oppositionspartei EZema gibt Pressekonferenz
ምስል DW/Y. Geberegziabher

ተጠርጣሪዎች ከመታሰራቸዉ በፊት በቂ ምክንያት መኖሩ በደንብ ይጣራም ሲል ጠይቆአል


የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በሲዳማ ዞን "ኢመደበኛ" ባላቸዉ ቡድኖች በዜጎች ላይ ጉዳት ሲደርስ ግፊት ያደረጉ ኃይሎች ለደረሰዉ መጠነ ሰፊ ጉዳት ኃላፊነት ሊወስዱ ይገባል አለ። የድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎች ዛሬ በሰጡት መግለጫ መንግሥት በአጥፊዎቹ ላይ "ጠንካራ ርምጃ" እንዲወስድ እንዲሁም ሰላማዊ ዜጎችን ከጥቃት እንዲከላከል ጠይቋል። ፓርቲዉ የዜጎች የመብት ጥያቄ በዘላቂነት የሚፈታዉ በሠላማዊ መንገድ ብቻ ነዉ ብሎአል። "በአሁኑ ወቅት ከተለያዩ ፖለቲካዊ ክስተቶች እና ግጭቶች ጋር ተያይዞ በወንጀል ተጠርጥረው የሚታሰሩ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል" ያለው ኢዜማ "አልፎ አልፎ የኢዜማ አባላትም የእስሩ ሰለባ ሆነዋል" ሲል በመግለጫው ጠቁሟል። በወንጀል የተጠረጠሩ ሕግ ፊት መቅረባቸዉ ተገቢ መሆኑን ብናምንም ፤ ተጠርጣሪዎች ከመታሰራቸዉ በፊት ለእስር የሚያበቃ በቂ ምክንያት አለበት ሲል ባወጣዉ መግለጫ አሳስቧል። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን መግለጫዉን ተከታትሎ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል። 


ዮሃንስ ገብረ እግዚአብሔር

አዜብ ታደሰ
ተስፋለም ወልደየስ