1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሳምንታዊ መግለጫ  

ሐሙስ፣ የካቲት 17 2014

ኤች አር 6600 የተባለው የአሜሪካን ም/ቤት ረቂቅ ሕግ ኢትዮጵያ ምላሽ የሰጠችባቸውን ጥያቄዎች የሚያነሳና የራሳቸውን ፍላጎት ለማሳካት የተረቀቀ ነው ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ። ረቂስ ሕጉ ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ምርመራ፣ከሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት እንቅፋት መሆን ጋር በተገናኙ ጉዳዮች ላይ ኢትዮጵያን ተጠያቂ ለማድረግ የተረቀቀ መሆኑ ተሰምቷል።

https://p.dw.com/p/47YGp
Amabassdor Dina Mufti (Ministry of Ethiopian foreign affairs spokesperson)
ምስል Solomon Muche/DW

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ


የአሜሪካ ምክር ቤት ኢትዮጵያን አስመልክቶ ዐዲስ ያወጣው ኤች አር 6600 የተባለው ረቂቅ ሕግ ኢትዮጵያ ምላሽ የሰጠችባቸውን ጥያቄዎች የሚያነሳ እና የራሳቸውን ፍላጎት ለማሳካት የተረቀቀ ነው ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ። ረቂስ ሕጉ ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ምርመራ ፣ ከሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት እንቅፋት መሆን ጋር በተገናኙ ጉዳዮች ላይ ኢትዮጵያን ተጠያቂ ለማድረግ የተረቀቀ መሆኑ ተሰምቷል።በሌላ በኩል የሚኒስቴሩ ቃል ዐቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በብራሰልሱ የአፍሪቃ - አውሮጳ ሕብረቶች ጉባኤ ላይ የተሳተፈችው ኢትዮጵያ ከየአገራቱ ጋር የሁለትዮሽ የተናጠል ፍሬያማ ውይይቶችን እንድታካሂድ እድል እንደፈጠረላት ተናግረዋል።
 
ሰሎሞን ሙጬ 


ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ