የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በትግራይ ያደረገው ድጋፍ
ረቡዕ፣ የካቲት 17 2013ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በትግራይ ክልል እስካሁን ከ ሦስት መቶ ሺህ ላልበለጠ ተረጂ ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ።ማሕበሩ ድጋፍ አሰባስቦ ከዚህ በላይ ለመድረስ ውጥን እንዳለው ገልጻል። በተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የኢትዮጵያ ቢሮ በበኩሉ በተለይም በክልሉ ለሚገኙ ስደተኞች አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጾ ነገር ግን አሁን ድረስ ሊደርሱባቸው ያልቻሉ ሥፍራዎች እንዳሉ እና የግንኙነት አውታሮች ሙሉ በሙሉ ክፍት አለመሆን የሰብዓዊ ድጋፍ ሁኔታውን አሳሳቢ እንዳደረገው ተናግረዋል።
ሰለሞን ሙጬ
ታምራት ዲንሳ
ኂሩት መለሰ