1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«በሱዳን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ በክብር ሊወጣ ይገባል» ኢትዮጵያ

ሐሙስ፣ ሰኔ 24 2013

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከተባበሩት መንግሥታት የምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ እና የሰላም ግንባታ ዳይሬክተር ጋር ከሰሞኑ በጉዳዩ ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በሳውዲ አረቢያ በእንግልት ላይ የሚገኙ አሥር ሺህ ዜጎች ወደ አገር ውስጥ መግባታቸውንም በመግለጫቸው ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/3vt0L
Äthiopien Botschafter Dina Mufti
ምስል Solomon Muchie/DW

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋዜጣዊ መግለጫ

በሱዳን አቢዬ ግዛት የሰፈረው የኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪ ኃይል ከተልዕኮው የሚወጣ ከሆነ ተገቢ ፣ ተመጣጣኝ እውቅና እና አክብሮት ተሰጥቶት ሊሆን እንደሚገባ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይህንን ያለው ሱዳን ሰላም አስከባሪው ኃይል ከግዛቱ ለቅቆ እንዲወጣ ጥያቄ ካቀረበች በኋላ ነው።ኢትዮጵያ በሰላም አስከባሪዎችዋ በተባበሩት መንግሥታት በኩል ከፍተኛ እውቅና አላት ያሉት የሚኒስቴሩ ቃል ዐቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከተባበሩት ማንግሥታት የምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ እና የሰላም ግንባታ ዳይሬክተር ጋር ሰሞኑን በዚሁ ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል።ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በሳዑዲ አረቢያ በእንግልት ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለማምጣት እስካሁን በተደረጉ 35 በረራዎች አሥር ሺህ የሚደርሱ ዜጎች ወደ አገር ውስጥ መግባታቸውንም ቃል ዐቀባዩ በመግለጫቸው ተናግረዋል።ጋዜጣዊ መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ሰሎሞን ሙጬ ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል።

ሰሎሞን ሙጬ

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ