የኢትዮጵያ ምርጫና ውዝግቡ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 28 2013ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ዉስጥ «ምርጫ ይደረግ አይደረግ» ዉዝግብ እዚያዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚሰሩ የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎችንም እያወዛገበ ነዉ።ገዢዉ ፓርቲና መንግስት አደረሱብን ባሉት ጫና ምክንያት እራሳቸዉን ከምርጫዉ ያገለሉት ተቃዋሚ ፖለቲከኞች አሁንም ኢትዮጵያን ለገጠሟት ችግሮች ከብሔራዊ ድርድርና መግባባት የተሻለ አማራጭ የለም እያሉ ነዉ።በምርጫዉ የሚሳተፉት ተቃዋሚና የገዢዉ ፓርቲ ፖለቲከኞች ግን ብሔራዊ ድርድርና የብሔራዊ የአንድነት መንግስት የሚለዉን ሐሳብ አይቀበሉትም።
ስዩም ጌቱ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ