1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ መንግስት ወቀሳ

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 5 2014

የሚንስቴሩ ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት በመጪዉ ሰኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሊደረግ የታቀደዉ ዓለም አቀፍ የቴሌኮሙኒኬሽን ስብሰባ ወደ ሌላ ሐገር እንዲዛወር ቅስቀሳ እየተደረገ ነዉ።

https://p.dw.com/p/44FtD
Äthiopien Hawassa | Ambassador Dina Mufti
ምስል Shewangizaw Wegayehu/DW

«በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫናዉ ቀጥሏል» አምባሳደር ዲና

ምዕራባዉያን መንግስታት በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የሚያደርጉት ግፊትና ጫና አሁንም መቀጠሉን የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር አስታወቀ። የሚንስቴሩ ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት በመጪዉ ሰኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሊደረግ የታቀደዉ ዓለም አቀፍ የቴሌኮሙኒኬሽን ስብሰባ ወደ ሌላ ሐገር እንዲዛወር ቅስቀሳ እየተደረገ ነዉ። የአዉሮጳ ሕብረት በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ላይ የሚነጋገር ስብሰባ ነገ ጄኔቭ-ሲዊትዘርላድ ዉስጥ እንዲደረግ መጥራቱንም አምባሳደር ዲና አሳዛኝ ብለዉታል። የዓለም ጤና ድርጅት (WHO)ን ጨምሮ የተባበሩት መንግሥታት የተለያዩ ድርጅቶች በአማራና በአፋር ክልሎች በሚገኙ ተቋማት ላይ የደረሰዉን ጥፋት በዝምታ አልፈዉታል በማለት ወቅሰዋልም።

ሰለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ