1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ኅብረት መሪዎች አስቸኳይ ጉባዔ መጠናቀቅ

ሰኞ፣ ኅዳር 10 2011

የአፍሪቃ ኅብረት ሁለት ዓመት ያህል ሲመክርበት የነበረውን የተሀድሶ እቅድ ወደፊት ለማራመድ በአዲስ አበባ ያካሄደው የሁለት ቀናት አስቸኳይ የመሪዎች ጉባዔ ተጠናቀቀ። ከ40 የሚበልጡ የሀገር መሪዎች የተሳተፉበት ይኸው አስቸኳይ ጉባዔ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

https://p.dw.com/p/38WGU
Äthiopien AU-Gipfel in Addis Adeba
ምስል Getty Images/AFP/M. Bhuiyan

የአፍሪቃ ህብረት እና የተሀድሶ ጥረቱ


የኅብረቱን የስራ ዘርፎቹን በአዲስ መልክ ለማዋቀር፣ ዓመታዊ መዋጮዋቸውን በማይከፍሉ አባል ሀገራትም ላይ ማዕቀብ ለመጣል ወስኗል። ይህን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችለው ቴክኒካዊ ጥናትም መዘጋጀቱን አስታውቋል።  በአስቸኳዩ ጉባዔ ላይ የተደረሱትን ውሳኔዎች ህብረቱ ከአንድ ወር ተኩል በኋላ በአዲስ አበባ በሚያደርገው አጠቃላይ ስብሰባ ላይ ለጽድቂያ እንደሚያቀርብ አመልክቷል። 

ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

አርያም ተክሌ

ማንተጋፍቶት ስለሺ