1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዉሮጳ ሕብረት የበጀት ድጎማ ዕቀባ

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 8 2013

የሕብረቱ ባለስልጣናት ዛሬ በሰጡት ዘርዘር ያለ ማብራራያ የተያዘዉ ርዳታ የኢትዮጵያ ክልልሎችን ለማገናኘት፣ ለጤና እና ለስራ ዕድል መርሐ ግብር መስኮች መንግሥት ለሚመድበዉ በጀት መደጎሚያ የሚዉል ነበር

https://p.dw.com/p/3mskG
Symbolbild  EU-Wiederaufbaufonds
ምስል Imago Images/C. Ohde

የአዉሮጳ ሕብረት ለኢትዮጵያ የሚሰጠዉን ርዳታ ያቀበበት ምክንያት

የአዉሮጳ ሕብረት ለኢትዮጵያ መንግስት በጀት መደጎሚያ ሊሰጠዉ የነበረዉን የ90 ሚሊዮን ዩሮ ርዳታ ለሌላ ጊዜ መግፋቱን ትናንት ዘግበን ነበር።ሕብረቱ ርዳታዉን የያዘዉ በትግራዩ ዉጊያ ሰበብ መሆኑን ገልጧልም።የሕብረቱ ባለስልጣናት ዛሬ በሰጡት ዘርዘር ያለ ማብራራያ የተያዘዉ ርዳታ የኢትዮጵያ ክልልሎችን ለማገናኘት፣ ለጤና እና ለስራ ዕድል መርሐ ግብር መስኮች መንግሥት ለሚመድበዉ በጀት መደጎሚያ የሚዉል ነበር።የሕብረቱ ባለስልጣናት እንዳስታወቁት የተያዘዉ በጀት የሚለቀቀዉ ሕብረቱ ያስቀመጣቸዉ ቅድመ ሁኔታዎችን የኢትዮጵያ መንግስት ሲያሟላ ነዉ።

ገበያዉ ንጉሴ 

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ