የአክሱም ሐውልት ጥገና
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 16 2012ማስታወቂያ
የአክሱም ሐውልት ጨምሮ ሌሎች በአካባቢው ያሉ ቅርሶች በከፋ አደጋ ላይ እንደሚገኙ የቅርስ ጥበቃ ባለሙያዎችና የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ፡፡ሐውልቱን የጎበኘው የመቀሌው ዘጋቢያችን ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ እንደሚለው በተለይ ለ1600 ዓመት ገደማ ከተተከለበት ቦታ ሳይንቀሳቀስ የቆየው በባለሙያዎች ቁጥር 3' ተብሎ የሚታወቀው የአክሱም ሐወልት ወደ ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ ዘሞ ይታያል፡፡ለሐውልቱ ይደረጋል የተባለው ጥገናም አሁን ድረስ አልተጀመረም፡፡የኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን በበኩሉ የአክሱም ሐወልት አደጋ ላይ መሆኑ በመግለፅ ቅርሱ ለመጠገን የተደረገው ዝግጅት ተጠናቆ ከመጪው ጥር ወር ጀምሮ ተግባራዊ ስራ ይጀመራል ብሏል፡፡
ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ