የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ትዕዛዝት
ዓርብ፣ ኅዳር 17 2014ማስታወቂያ
የፀጥታ አስከባሪ አካል ሳይሆኑ የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብሶች ለብሰው የሚገኙ እና የሽግግር መንግሥት እንመሰርታለን በሚል የሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የፀጥታ አካላት ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ትናንት ትዕዛዝ አስተላልፏል። ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ፣ የጦር ሜዳ ውሎዎችን እና ውጤቶችን በተመለከተ ሥልጣን ከተሰጠው አካል ውጪ በየትኛውም የመገናኛ አውታር መግለጫዎችን መስጠትና ማሰራጨትም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዙ ተከልክሏል።ዕዙ የሀሳብ ነፃነትን ሰበብ በማድረግ ልዩ ልዩ የሚዲያ አውታሮችን በመጠቀም የሽብር ቡድኑን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በመደገፍ በህልውና ዘመቻው ላይ እንቅፋት የሚፈጥሩ ያላቸው አካላትም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አስጠንቅቋል።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሰ