1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአሜሪካ ባለሥልጣናት ተደጋጋሚ የኢትዮጵያ ጉብኝት

ዓርብ፣ ነሐሴ 7 2013

ከመደበኛው የውጭ ጉዳይና የኤምባሲ አካሄድ በዘለለ በአሜሪካ የውጭ ግንኙነት አሠራር ልዩ መልዕክተኛ ወደ አንድ አገር ሲላክ ፕሬዝደንቷ ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን ማሳያ መሆኑን አንድ የፖለቲካ ሳይንስ ዐዋቂ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። በሌላ በኩል ደግሞ አሜሪካ ጉዳዩን ወደ ድርድር የመውሰድ ፍላጎቷ ላለመሳካቱ ማሳያም ሊሆን ይችላል። 

https://p.dw.com/p/3yxtn
USA Jeffrey Feltman in New York
ምስል picture-alliance/Pacific Press/A. Lohr-Jones

የተደጋገመው የአሜሪካ ባለሥልጣናት ጉብኝት

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ምልዕክተኛ በሦስት ወራት ልዩነት ውስጥ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚሄዱ ይጠበቃል። ከመደበኛው የውጭ ጉዳይ እና የኤምባሲ አካሄድ በዘለለ በአሜሪካ የውጭ ግንኙነት አሠራር ልዩ መልዕክተኛ ወደ አንድ አገር ሲላክ በአገሪቱ ፕሬዝዳንት ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን ማሳያ መሆኑን አንድ የፖለቲካ ሳይንስ ዐዋቂ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። እንደእሳቸው በሌላ በኩል ደግሞ አሜሪካ ጉዳዩን ወደ ድርድር የመውሰድ ፍላጎቷ ላለመሳካቱ ማሳያ ሊሆንም ይችላል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የብሔራዊ ፀጥታ አማካሪ የልዩ መልዕክተኛውን ጉብኝት አስመልክቶ በማኅበራዊ መገናኛቸው ሁሉም ወገኖች በአስቸኳይ ወደ ድርድር እንዲቀርቡ ጠይቀዋል። ዋናው መፍትሔ መንግሥት ሰላምና የዜጎች ደህንነትን ማስጠበቁ ነው ያሉት አስተያየት ሰጪው የአሜሪካ እየተለወጠ ያለ የምሥራቅ አፍሪካ የወዳጅነት አሰላለፍ ኢትዮጵያን ለተጨማሪ ጫና ሊዳርጋት እንደሚችልም ገልፀዋል።

ሰሎሞን ሙጩ
ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ