1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) የምርጫ ዝግጅት

ሰኞ፣ ጥር 17 2013

ፓርቲው ትናንት ከአባላቱ ጋር በባህርዳር ባካሄደው ውይይት ማንኛውንም የአመፅ እንቅስቃሴ እንደሚቃወም ገልጾ፣ አባላቱና ደጋፊዎቹም ከዚህ እንዲቆጠቡ ግንዛቤ እያስጨበጥኩ ነው ብሏል። ዲሞክራሲ እንዲያሸንፍ እንሰራለን የሚለው ፓርቲው በምርጫ ቢሸነፍ እንኳን በጸጋ ተቀብሎ በቀጣዩ ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ የሚሆንበትን መንገድ እንደሚፈልግ አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/3oOa7
Äthiopien Amhara Democratic Forces Movement
ምስል Alemnew Mekonnen/DW

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) የምርጫ ዝግጅት


 

ቀጣዩ ብሔራዊ ምርጫ ነፃና ፍትሀዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን)አስታወቀ።ፓርቲው ትናንት ከአባላቱ ጋር በባህርዳር ባካሄደው ውይይት ማንኛውንም የአመፅ እንቅስቃሴ እንደሚቃወም ገልጾ፣ አባላቱና ደጋፊዎቹም ከዚህ እንዲቆጠቡ ግንዛቤ እያስጨበጥኩ ነው ብሏል። ዲሞክራሲ እንዲያሸንፍ እንሰራለን የሚለው ፓርቲው በምርጫ ቢሸነፍ እንኳን በጸጋ ተቀብሎ በቀጣዩ ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ የሚሆንበትን መንገድ እንደሚፈልግ አስታውቋል።ከሁለት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ የገባው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) በዘንድሮው ምርጫ ፓርቲው ወክለው የሚወዳደሩ 414 እጩ ተወዳዳሪዎችን አንደሚያቀርብ አስታውቋል። አለምነው መኮንን ከባህርዳር ቀጣዩን ዘገባ አዘጋጅቷል።
አለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ