1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የትግራይ ምሁራን ዓለም አቀፍ ጉባኤ

ሰኞ፣ ሐምሌ 22 2011

 ከ25  የዓለም  ሃገራት የተውጣጡ 2 000 ምሁራን የሚሳተፉበት ዓለም አቀፍ  የትግራይ  ምሁራን  ጉባኤ  በመቐለ  በመካሄድ ላይ ነው። ትናንት በተጀመረው ጉባኤ ምሁራኑ ላለፈው አንድ ዓመት ያካሄዷቸውን  ጥናቶች  በማቅረብ ላይ ናቸው።

https://p.dw.com/p/3MuVC
Äthiopien - Internationale Große Konferenz der Tigriyan-Gelehrten
ምስል DW/M. Hailesillasie

«ከ2000 በላይ ምሁራን ይሳተፋሉ»

ጥናቶቹ ያተኮሩት  በ14 የተመረጡ ዘርፎች ላይ ሲሆን የክልሉ መንግሥት ለምሁራኑ ባቀረበው ጥሪ መሠረት ለስትራቴጂክ ዕቅዶች ግብአት የሚሆኑ ሃሳቦች እንደሚቀርቡበት የጉባኤው አስተባባሪ ኮሚቴ ሊቀመንበር ለዶይቼ ቬለ DW ገልጸዋል። ጉባኤው እስከ ሐምሌ 25 ቀን 2011 ዓ,ም ድረስ የሚቆይ ይሆናል። 
ትናንት እሁድ በተጀመረው  ዓለም አቀፍ  የትግራይ  ምሁራን  ስብሰባ በ200  ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ  ተቋማት  የሚሠሩ ተሳታፊዎች  ተገኝተዋል። ከተሳታፊ እና ጥናት አቅራቢ ምሁራኑ መካከል 600ዎቹ  PHD ያላቸው ሲሆኑ ሌሎች 120 ደግሞ PHD ተማሪዎች መሆናቸውን የጉባኤው አስተባባሪዎች ተናግረዋል። ካለፈው ዓመት ክረምት ጀምሮ በ14 የተመረጡ ዘርፎች ጥናት ሲያደርጉ የቆዩት እነዚህ ምሁራን በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢነርጂ፣ ሚድያና ኮምኒኬሽን እንዲሁም ሌሎች ርእሰ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ የጥናት ውጤቶች እያቀረቡ ነው። 
የዓለም አቀፍ ምሁራን ኮንፈረንስ አስተባባሪ ኮሚቴ ሊቀ መንበርና የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝደንት ዶክተር ኪሮስ ጉዑሽ መድረኩ የትግራይ ክልል መንግሥት ለምሁራን ባቀረበው ጥሪ መሠረት እየተደረገ ያለ መሆኑ በመግለፅ ለስልታዊ ዕቅዶች ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦች እንደሚቀርቡበት አመልክተዋል። 
በጉባኤው መክፈቻ ስነ ስርዓት  ላይ ተገኝተው  ንግግር  ያደረጉት  የትግራይ  ክልል  ምክትል  ርእሰ  መስተዳድር  ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በምሁራኑ  አነሳሽነትና  ድጋፍ  የተለያዩ  የመንግሥት ተቋማት እየተቋቋሙ መሆኑ ገልፀዋል። በ2011 ዓ,ም የትግራይ ፖሊሲ  ጥናት እና ምርምር  ኢንስትቲትዮት፣ የትግራይ  ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣  የትግራይ  ስታስቲክስ  ኤጀንሲ እና ሌሎች ተቋማት መመሥረታቸውን  የገለፁት  ዶክተር  ደብረፅዮን  እነዚህ  የምሁራኑ ጥናት  ተቋማዊ  በሆነ  ሁኔታ  ለመጠቀም   ዕድል የሚፈጥሩ ዕድል የሚፈጥሩ ናቸው ብለዋል። የምሁራን  ኮንፈረንሱ አስተባባሪዎች እንደነገሩን በአንድ የትኩረት ዘርፍ ብቻ እስከ 20 የመፍትሔ ሐሳቦችና ጥናታዊ ፅሑፎች እየቀረቡ ነው፡፡ ኮንፈረንሱ እስከ ሐምሌ 25 ድረስ ይዘልቃል።  
ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ

Äthiopien - Internationale Große Konferenz der Tigriyan-Gelehrten
ምስል DW/M. Hailesillasie

ሸዋዬ ለገሠ

 እሸቴ በቀለ