1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የታጣቂዎች ጥቃት በነጆ ወረዳ

ማክሰኞ፣ ግንቦት 17 2013

ባለፈው አርብ ሌሊት 10 ሰዓት ገደማ  ከቤኒንል ጉሙዝ ከልል ተሻገሩ የተባሉ ታጣቂዎች በምእራብ ወለጋ ነጆ ወረዳ  ጥቃት ማድረሳቸውን የነጆ ወረዳ አስተዳደር ዐስታውቋል። በነጆ ወረዳ ያምበልጋራ ኦሊ በተባለ ቀበሌ  ውስጥ ደረሰ በተባለው ጥቃት የስድስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የነጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታሊላ ተረፋ በስልክ ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/3twBp
Mendi city
ምስል DW/N. Desalegn

ዳግም ጥቃት

ባለፈው አርብ ሌሊት 10 ሰዓት ገደማ  ከቤኒንል ጉሙዝ ከልል ተሻገሩ የተባሉ ታጣቂዎች በምእራብ ወለጋ ነጆ ወረዳ  ጥቃት ማድረሳቸውን የነጆ ወረዳ አስተዳደር ዐስታውቋል። በነጆ ወረዳ ያምበልጋራ ኦሊ በተባለ ቀበሌ  ውስጥ ደረሰ በተባለው ጥቃት የስድስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የነጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታሊላ ተረፋ በስልክ ተናግረዋል። ታጣቂዎቹ በሰው ላይ ካደረሱት ጉዳት በተጨማሪም ቤት ማቃጠላቸውን እና ከብቶችም ዘርፈው መሰወራቸውን አቶ ታሊላ አክለዋል። ፖሊስ ወደ ስፋራው ካቀና በኋላ ከነዋሪው ባገኘው መረጃ መሠረት፦ በነጆ ወረዳ ቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው በቤኒንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ በሚገኝና አጎራባች ወረዳ በሆነው ስርባባይ በተባለ ስፍራ ታጣቂዎቹ ሲንቀሰቀሱ እንደነበር ማረጋገጣቸውን አመልክቷል።

ነጋሣ ደሳለኝ


ማንተጋፍቶት ስለሺ
ሸዋዬ ለገሰ