የተፈናቃዮች አቤቱታ በአማራ ክልል
ዓርብ፣ ሚያዝያ 8 2013ማስታወቂያ
ከኢትዮ ሱዳን የድንበር ግጭት ጋር ተያይዞ በሱዳን የተለያዩ ግዛቶች ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከሚኖሩባቸው አካባቢዎች እንዲወጡ እየተደረጉ መሆኑን አመለከቱ። ከተለያዩ የሱዳን ግዛቶች ወደ መተማ የገቡት እነዚህ ወገኖች አስፈላጊው ድጋፍ እንዳልተደረገላቸውም እየተናገሩ ነው፡፡ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ከተማ አስተዳደር ቅሬታው ትክክል መሆኑን ሲያረጋግጥ፤ የዞኑ አደጋ መከላከል መሥሪያ ቤት በበኩሉ ድጋፍ ለማድረግ ተዘጋቻለሁ እያለ ነው።
ዓለምነው መኮንን
ሸዋዬ ለገሠ
ማንተጋፍቶት ስለሺ