1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተወካዮች ም/ቤት 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ እንዲካሄድ ወሰነ

ማክሰኞ፣ መስከረም 12 2013

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ጉባዔ ስድስተኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ በዚህ ዓመት እንዲከናወን ወሰነ።ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው  ምርጫውን ከተመለከተው ውሳኔ በተጨማሪ በኮሮና ተኅዋሲ ምክንያት ታግደው የነበሩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብሮች በጥንቃቄ እንዲከናወኑም ፈቅዷል።

https://p.dw.com/p/3iqI3
Repräsentantenhaus in Äthiopien
ምስል DW/Y. Gebreegiziabher

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ይካሄድ ዘንድ ይሁንታውን ሰጠ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ጉባዔ ስድስተኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ በዚህ ዓመት እንዲከናወን ወሰነ።ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው  ምርጫውን ከተመለከተው ውሳኔ በተጨማሪ በኮሮና ተኅዋሲ ምክንያት ታግደው የነበሩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብሮች ማለትም የሕዝብ ስብሰባዎች፣ ክብረ በዓላት ፣ የስፖርት ፣ የትራንስፖርት እና የቱሪዝም እንቅስቃሴዎች በከፍተኛ ጥንቃቄ ውስጥ ሆነው እንዲከናወኑ በአንድ ተቃውሞና በስምንት ድምፅ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።በተጨማሪም የሚኒስትሮችንና የፌደራል ፍርድ ቤት እጩ ዳኞችን ሹመትም አፅድቋል።

ሰለሞን ሙጬ

ታምራት ዲንሳ

እሸቴ በቀለ