1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የባህርዳሩ የገና ገበያ 

ሰኞ፣ ታኅሣሥ 29 2011

የገና በዓል በመላ የክርስትና ተከታዮች ዘንድ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡ የበዓሉን ታሪካዊ አመጣጥና አከባበር እንዲሁም የበዓሉ ዝግጅት ከዋዜማው ጀምሮ በባህርዳርና አካባቢው ምን እንደሚመስል፣ ወኪላችን ዓለምነዉ መኮንን ቃኝቶአል።

https://p.dw.com/p/3B9Ph
Markt in Bahr Dar
ምስል DW/A. Mekonnen

በዓሉን ስናከብር ለሌላቸው በማካፈል መሆን አለበት


በከተማዋ  ለእርድ የቀረቡ እንስሳት  ገበያ እንዲሁም በዓሉን ስናከብርም የክርስቶስን መወለድ እያሰብን ያለንን ለሌላቸው በማካፈል መሆን እንዳለበት በከተማዋ ነዋሪ የሆኑት መምህር ንጉሱ አይተነው ተናግረዋል። መምህር ንጉሱ አይተነው በባህር ዳር ከተማ ምስራቀ ፀሐይ አዲሱ ሚካኤል የሰበካ ጉባዔ ምምህር ናቸው፡፡ መምህር ንጉሡ አንደሚሉት፣ የክርስቶስ ልደት በዓለም ደረጃ መከበር የጀመረው በንጉስ ቆስጠንጢኖስ ዘመነመንግስት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ደረጃ በዓሉ መከበር የጀመረው ከንጉስ ዘረዐአ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ጀምሮ በዋናነት በቤተ-ክርስቲያን ብቻ አንደነበር ጠቅሰው ቀስ በቀስ ወደ ህዝብ አንደሰፋም አስረድተዋል፡፡ 
 
ዓለምነው መኮንን  
አዜብ ታደሰ 
አርያም ተክሌ