የቀኝ ፅንፈኛ ሽብር በሃናው ከተማ
ሐሙስ፣ የካቲት 12 2012ማስታወቂያ
በትላንትናው ዕለት በምሥራቃዊ የራየን ማየን አካባቢ በምትገኘው ሃናው ከተማ አንድ የቀኝ ፅንፈኛ አክራሪ የ 43 ዓመት ጀርመናዊ ጎልማሳ በሁለት የሺሻ ማጨሻ ቤቶች ላይ በከፈተው የተኩስ ጥቃት 11 ሰዎች መግደሉን የጀርመን ፖሊስ አስታውቋል:: ግለሰቡ ከጥቃቱ በኋላ የወላጅ እናቱን እና የራሱን ሕይወት ማጥፋቱም ተገልጿል:: በጥቃቱ በርካታ የቱርክ ተወላጆች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን የገለጹት የቱርክ ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ ድርጊቱን በማውገዝ የጀርመን ባለስልጣናት አስፈላጊውን የህግ እርምጃ እንዲወስዱ በቲውተር ገጻቸው አሳስበዋል:: በርካታ ሰዎችም ከጥቃቱ በኋላ ሃዘናቸውን እና ድንጋጤያቸውን እየገለጹ ነው::
እንዳልካቸው ፈቃደ
ሸዋዬ ለገሠ
ኂሩት መለሰ