1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶሪያ ድብደባን በተመለከተ ቃለ መጠይቆች

ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 6 2010

ዩናይትድ ስቴትስ፣ ፈረንሣይ እና ብሪታንያ ዛሬ ማለዳ ከ100 በላይ ሚሳይሎችን በማስወንጨፍ ድብደባ ፈጸሙ። ጀርመን በድብደባው ባትሳተፍም ድጋፏን ገልጣለች። የዛሬው ድብደባን በተመለከተ የጀርመን ፖለቲከኞች ምን አሉ? የመካከለኛው ምሥራቅ እና ዓረብ ሃገራትስ?

https://p.dw.com/p/2w3q4
Syrien Krieg - Damaskus nach Angriff durch die USA, Frankreich & Großbritannien | Scientific Research Centre
ምስል Reuters/O. Sanadiki

የሶሪያ መደብደብን በተመለከተ ቃለ መጠይቅ ከበርሊን

ዩናይትድ ስቴትስ፣ ፈረንሣይ እና ብሪታንያ ዛሬ ማለዳ ከ100 በላይ ሚሳይሎችን በማስወንጨፍ ድብደባ ፈጽመዋል። የሶሪያ አጋር ሩስያ ድብደባውን በማውገዝ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ጥበቃ አስቸኳይ ስብሰባ እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፋለች። በአስቸኳይ ስብሰባው ግን ሩስያ ድብደባው እንዲወገዝ ያቀረበችው ጥያቄ 8 ለ3 በኾነ ድምፅ ውድቅ ኾኗል። ዩናይትድ ስቴትስን ጨምሮ ሦስቱ ሃገራት ሩስያን በሚሳይል የደበደቡን የበሽር አል አሳድ መንግሥት መርዛማ ንጥር ጦር መሣሪያዎችን ተጠቅሟል በሚል ነው። ድብደባው ተፈጸመ የተባለውም ንጥረ ነገሮቹ ተከማችተው ይገኙባቸዋል በተባሉ ሥፍራዎች እንደኾነ ተገልጧል። ጀርመን በድብደባው ባትሳተፍም ድጋፏን ገልጣለች። የዛሬው ድብደባን በተመለከተ የጀርመን ፖለቲከኞች ምን አሉ? የመካከለኛው ምሥራቅ እና ዓረብ ሃገራትስ?  

ቃለመጠይቆቹን ከታች በሚታዩት የድምፅ ማእቀፎች ውስጥ ይገኛሉ።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ይልማ ኃይለሚካኤል

ስለሺ ሽብሩ