1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰኔ 15 ተጠርጣሪዎች የችሎት ውሎ

ሰኞ፣ ሐምሌ 29 2011

ከሰኔ 15ቱ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ግድያ ጋር በተገናኘ ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት እነ ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞን ጨምሮ 53 ሰዎች ጉዳይ በፍርድ ቤት መታየት ጀመረ። ፖሊስ እስካሁን የ28 ምስክሮችን ቃል መቀበሉን፤፣ የሰነድ እና ቴክኒክ ማስረጃዎችም መሰብሰቡን አመልክቷል።

https://p.dw.com/p/3NNGl
Äthiopien Gerichtshof in Bahir Dar
ምስል DW/A. Mekonnen

«ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ ጊዜ ውድ ተደረገ»

እንዲያም ሆኖ ሌሎች ምስክሮችን ቃል ለመቀበልም ሆነ ተጨማሪ ማስረጃዎችን ለማሰባሰብ ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል። የተጠርጣሪ ጠበቆች ባንፃሩ ደንበኞቻቸውን ለማጉላላት ነው በሚል በመቃወማቸው ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን በማድመጥ የተጠየቀውን ተጨማሪ ጊዜ ውድቅ ማድረጉን ከባሕር ዳር ዘጋቢያችን ዓለምነው መኮንን በላከው ዜና አመልክቷል።

በተጠቀሰው ቀን ውስጥ አቃቢ ሕግ ክስ እንዲመሰረትና ታራሚዎችም  ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። በሰኔ 15ቱ ጥቃት በአማራ ክልል ድርጊቱን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 218 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው ሲጣራ ከቆየ በኋላ አብዛኛዎቹ መፈታታቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አበረ አዳሙ ሰሞኑን ገልፀው ነበር፣ ሆኖም ድርጊቱ ውስብስብና የሚሳሳብ በመሆኑ ተጠርጣሪዎች አሁንም እየተያዙ እንደሆነ ከዶየቼ ቬለ ራዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ አመልክተዋል። ሰኔ 15/2011 ጀኔራል አሳምነው ጽጌ መርተውታል በተባለውና የኢትዮጵ መንግስት መፈንቅለ መንግሥት ብሎ በጠራው ድርጊት የአማራ ክልል ርአስ መስተዳድር ነበሩት ዶ/ር አምባቸው መኮንንና ሌሎች ሁለት ከፍተኛ የክልሉ ባለስልታናት፣ ከቀናት በኋላ ደግሞ የድርጊቱ ጠንሳሽ ናቸው የተባሉት ብርጋደየር ጀኔራል አሳምነው ፅጌ መገደላቸው ይታወሳል።

ዓለምነው መኮንን

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ