1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰብዓዊ መብት ጥሰት መባባስ

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 17 2013

የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ሕብረት፦ መንግሥት አፋኝ የሚባሉ ሕግጋት በማሻሻል ተቋማትን ለሰብአዊ መብት ጥሰት ከመጠቀም በመቆጠብ ረገድ መልካም ሥራዎችን ቢያከናውንም የመብት ጥሰት ግን አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን አመለከተ።

https://p.dw.com/p/3kVnA
Äthiopien Addis Abeba
ምስል DW/S. Muchie

«የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ሕብረት»

የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ሕብረት፦ መንግሥት አፋኝ የሚባሉ ሕግጋት በማሻሻል ተቋማትን ለሰብአዊ መብት ጥሰት ከመጠቀም በመቆጠብ ረገድ መልካም ሥራዎችን ቢያከናውንም የመብት ጥሰት ግን አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን አመለከተ። የአንዱ ብሔር አባል የሌላውን፣ የአንዱ ቡድን አባልም እንዲሁ የሌላው ላይ ጥቃት የሚፈጽምበት፤ ጥቃቶቹም ከተፈጸሙ በኋላ ወደሕግ ይወሰዳል ይባላል፤ አንዳንድ አመራሮችም ላይ ርምጃ ለመውሰድ እንቅስቃሴ ይደረጋል ሆኖም ይህ ተቋማዊ ተደርጎ መፍትሄ ካልመጣለት በቀር የታሰበውን ዓላማ ሊመታ እንዳልቻለ የሰብዓዊ መብቶች ሕብረት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። ይኽ የመብት ጥሰት እና ጥቃት መሰረታዊ ችግር ኾኖ እንደሚታይም ተገልጧል። ሰለሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል።

ሰለሞን ሙጬ

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ