የምርጫ ቦርድ መግለጫ
ሰኞ፣ የካቲት 1 2013ማስታወቂያ
ክልሎች ቦርዱ የጠየቃቸውን ጽሕፈት ቤቶች ባለማሟላታቸው ሥራዬ ላይ እንቅፋት እየፈጠሩብኝ ነው ሲል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አማረረ። የቦርዱ ሊቀመንበር ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ዛሬ ከቀትር በኋላ አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ ለምርጫ አስፈጻሚዎች የሚሆኑ ጽሕፈት ቤቶች ባላሟሉ ክልሎች ከየካቲት ስምንት እስከ 21 ቀን 2013 ዓ,ም የእጩዎች ምዝገባ አይካሄድባቸውም ብሏል። መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዘገባ አለው።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር
ሸዋዬ ለገሰ
ነጋሽ መሐመድ