የመቀሌ ወቅታዊ ሁኔታ
ሰኞ፣ ሰኔ 21 2013ማስታወቂያ
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ለስምንት ወራት ገደማ ከባድ ውጊያ በተደረገበት የትግራይ ክልል የተኩስ አቁም እንዲደረግ ለመንግሥት ጥያቄ አቀረበ። ጊዜያዊ አስተዳደሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አብርሐም በላይ ለኢዜአ እንደተናገሩት ጥያቄውን ያቀረበው ባለፈው ሳምንት ነው። በክልሉ ዋና ከተማ መቐለ የትግራይ መከላከያ ሠራዊት ተብሎ የሚጠራው ኃይል ገብቷል የሚል መረጃ ከተሰራጨ በኋላ ነዋሪዎች ደስታቸውን መግለፅ ጀምረዋል።
ሚሊዮን ኃይለስላሴ
ነጋሽ መሐመድ