1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሕወሓትና የመከላከያ ሚንስቴር አስጥ አገባ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 20 2013

ቆቦ-ወልዲያ በተባለዉ አካባቢ ይደረጋል ስለሚባለዉ ዉጊያ የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት)ና የኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስቴር ተቃራኒ መግለጫ እየሰጡ ነዉ።

https://p.dw.com/p/3y8uG
Äthiopien Tigray-Krise
ምስል Stringer/File/REUTERS

የህወሃት መግለጫ

የሕወሓት ጦር አዛዦች ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ ተዋጊዎቻቸዉ ቆቦ ከተማን ጨምሮ የተለያዩ የአማራና የአፋር ክልል አካባቢዎችን መቆጣጠራቸዉን አስታዉቀዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስቴር ዛሬ እንዳስታወቀዉ ግን መከላከያ ሠራዊት እራሱን ከመከላከል ዉጪ እስካሁን ድረስ መንግሥት ያወጀዉን የተናጥል ተኩስ አቁም እንዳከበረ ነዉ። ይሁንና የመቀሌዉ ዘጋቢያችን ሚሊዮን ኃይለ ስላሴ የሕወሓት የጦር አዛዥ ጠቅሶ እንደዘገበዉ ሕወሓት በአማራና በአፋር ክልሎች ድል በማግኘቱ የኃይል ሚዛን የበላይነትን አግኝቷል። የመከላከያ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ለአዲስ አበበባዉ ወኪላችን ለስዩም ጌቱ እንደነገሩት የሕወሓት አማራና አፋር ክልል ተቀዳጀሁ ያለዉን ድል «ከሰርጎ ገብ ዘረፋ ያልዘዘ» በማለት አጣጥለዉታል።

ሚሊዮን ኃይለ ስላሴ/ ስዩም ጌቱ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ

 

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ