የሕወሓት መሪዎች ያሉበትን ለጠቆመ የገንዘብ ሽልማት
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 9 2013ማስታወቂያ
መከላከያ ሠራዊት የሕወሓት ከፍተኛ አመራሮች ያሉበትን ጥቆማ በመስጠት እንዲያዙ ለሚያደርጉ ሰዎች የአሥር ሚሊዮን ብር ሽልማት ማዘጋጀቱን ይፋ አደረገ። ጥቆማውን በዋናነት ሕግ ማስከበር ላይ ለተሰማሩ ለመከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል ፖሊስና የመረጃ ሰዎች በአካል ማድረስ እንደሚቻልም ተነግራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከሳምንታት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ተፈላጊዎቹ የሕወሓት ባለ ሥልጣናት ከተደበቁበት ቀንም ማታም በሰው አልባ በራሪ ቁስ ይከታተሏቸውና ያይዋቸው እንደነበር ተናግረው ነበር።
ሰሎሞን ሙጬ
ሸዋዬ ለገሠ
እሸቴ በቀለ