የሐጅ ፀሎተኞች ስሞታ
ረቡዕ፣ ነሐሴ 16 2010ማስታወቂያ
ለዘንድሮዉ የሐጅ ፀሎት ወደ መካ-ሳዑዲ አረቢያ የተጓዙ ኢትዮጵያዉያን ምዕመናን ከኢትዮጵያ ከመነሳታቸዉ በፊት እና ሳዑዲ አረቢያ ከደረሱም በኋላ ክፉኛ መገላታታቸዉን እየገለፁ ነዉ።የምዕመናኑን ስሞታ የተከታተሉ ወገኖች እንደዘገቡት የኢትዮዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞቹን ጉዞ አዘግይቶባቸዋል፤ ሳዑዲ አረቢያ ከደረሱም በኋላም በቂ ምግብ እና መጠለያ አላገኙም።ለሐጅ እዚያዉ ሳዑዲ አረቢያ የሚገኘዉ የፖለቲካ አቀንቃኝ እና የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ሥራ አስኪያጅ ጀወር መሐመድ እንደሚለዉ ለወደፊቱ የምዕመናኑን መንገላታት ለመቀነሰ አራት ወገኞች ተቀናጅተዉ መስራት አለባቸዉ።ነጋሽ መጐመድ ጀዋርን በስልክ አነጋግሮታል።
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ