የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ለኢትዮጵያ
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 14 2014ማስታወቂያ
በሰሜን ኢትዮጵያ ውድመትና ዘረፋ ለተፈፀመባቸው የጤና ተቋማት 18 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ የሕክምና ቁሳቁሶች ለማጓጓዝ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን ግሎባል ኤይድ ኢትዮጵያ አስታወቀ።
በካናዳ የግሎባል ኤይድ ኢትዮጵያ መስራችና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ደመም ለዶይቸ ቨለ እንደገለጹት የሕክምና ቁሳቁሶቹን ጂቡቲ ወደብ ለማድረስ የገንዘብ ማሰባሰብ ተካሄዶ እስካሁን ከ164 ሺህ ዶላር በላይ ተገኝቷል።
በሌላ በኩል በአሪዞና፣ በፊኒክስና አካባቢው እንዲሁም በሰሜን ካሮላይና የሚገኙ ኢትዮጵያን እና ትውልደ ኢትዮጵያን በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች መርጃ የሚውል ድጋፍ አሰባስበዋል።
ታሪኩ ኃይሉ
ታምራት ዲንሳ
ኂሩት መለሰ