ዋግኽምራ መብራት ተቋረጠ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 1 2013ማስታወቂያ
በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የኤሌክትሪክ መብራት በመቋረጡ የነዋሪዎችና የንግድ ተቋማት እንቅስቃሴ መታጎሉን ነዋሪዎች ዐስታወቁ። የዞኑ መስተዳድር እንዳስታወቀዉ በመስተዳድሩ ስር በሚገኙ በስምንት ወረዳዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከተቋረጠ ሁለተኛ ሳምንቱን ይዟል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሥሪያ ቤቶችም የሚሰጡት አገልግሎች መቋረጡን አምነዋል። ሁለቱ መሥሪያ ቤቶች እንደሚሉት መብራት የተቋረጠዉ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመዶች በመሰረቃቸዉና ምሰሶዎች በመውደቃቸው ነዉ።
ዓለምነዉ መኮንን
ነጋሽ መሐመድ
ማንተጋፍቶት ስለሺ