1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«ወደ ትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይደርስ ተደርጎአል የሚለዉ ክስ ተቀባይነት የለዉም»  መንግሥት

ሰኞ፣ ጳጉሜን 1 2013

መንግሥት ወደ ትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይደርስ ክልከላ እያደረገ ነው የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም ሲል የሰላም ሚኒስቴር ተናገረ። ረሃብን እንደ ጦር መሣሪያ መጠቀም የህወሓት ተፈጥራዊ ባህርይ ነው።

https://p.dw.com/p/3zyz7
Äthiopien Addis Abeba | Muferiat Kamil - Friedensministerin
ምስል Solomon Muchie/DW

«ረሃብን እንደ ጦር መሣሪያ መጠቀም የህወሓት ተፈጥራዊ ባህርይ ነው» መንግሥት

 

መንግሥት ወደ ትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይደርስ ክልከላ እያደረገ ነው የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም ሲል የሰላም ሚኒስቴር ተናገረ። መንግሥት የተናጠል ተኩስ አቁም ሲያደርግ ለትግራይ ሕዝብ የአንድ ወር፣ረጂ ድርጅቶችም የአንድ ወር በአጠቃላይ የሁለት ወር ምግብ አስቀምጦ መውጣቱን የሰላም ሚኒስትሯ ሙፈሪያት ካሚል ዛሬ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

በተጨባጭ ለህወሓት ምሣሪያ ፣ መድኃኒት እና ምግብ የሚያቀርቡ ድርጅቶች በመገኘታቸው መንግሥት ሁለት ዘመናዊ የተሽከርካሪ መፈተሻ ማሽኖችን መትከሉንም ገልፀዋል። ሆኖም ሰባት የነበሩት የፍተሻ ኬላዎች ወደ ሁለት ዝቅ መደረጋቸውንም ትናግረዋል።

ወደ ክልሉ እስካሁን 538 ተሽከርካሪዎች ሰብዓዊ ድጋፍ ጭነው መጓዛቸውን፣ ያም ሆኖ ግን 72 በመቶው ወደ ትግራይ የተጋዙት ተሽከርካሪዎች አለመመለሳቸው ይህም አሳሳቢ መሆኑን ገልፀዋል።

ህወሓት ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በከፈተው ጥቃት 4.5 ሚሊዮን ዜጎች ለችግር እንደተጋለጡ የተናገሩት የሰላም ሚኒስትሯ መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ወደ እነዚህ ክልሎች የሚቀርበው ሰብዓዊ ድጋፍ በቂ አይደለም ብለዋል።

ረሃብን እንደ ጦር መሣሪያ መጠቀም የህወሓት ተፈጥራዊ ባህርይ ነው ሲሉም ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ተናግረዋል።

 

ሰለሞን ሙጬ

አዜብ ታደሰ

ነጋሽ መሐመድ