1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኮቪድ 19 ሁለተኛ ዙር ወረርሽኝ በአውሮጳ

ዓርብ፣ ጥቅምት 20 2013

በአውሮጳ ዳግም በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ለመግታት የሕብረቱ አባል መንግሥታት ጥብቅ ርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው። የተሐዋሲው ስርጭት በየዕለቱ እየጨመረና እየተባባሰ መምጣቱ ሁሉንም የአውሮጳ ሃገራት አስጨንቋል።

https://p.dw.com/p/3kfGe
EU-Videogipfel zur Corona-Pandemie
ምስል Olivier Hoslet/EPA Pool/AP/dpa/picture alliance

«ለሰዓታት የቪዲዮ ስብሰባ አካሂደዋል»

 

በአውሮጳ ዳግም በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ለመግታት የሕብረቱ አባል መንግሥታት ጥብቅ ርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው። የተሐዋሲው ስርጭት በየዕለቱ እየጨመረና እየተባባሰ መምጣቱ ሁሉንም የአውሮጳ ሃገራት አስጨንቋል። በዚህም ምክንያት የሕብረቱ መሪዎች ትናንት በዚሁ ጉዳይ ላይ የቪዲዮ ጉባኤ አካሂደዋል።  ፈረንሳይና ጀርመንን ጨምሮ ብዙዎቹ አባል መንግሥታት መጠጥ ቤቶችና ምግብ ቤቶችን፤ የባህልና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፤ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲዎች እንዲዘጉ ወስነዋል። የሰዓት እላፊ አዋጅም ደንግገዋል። ገበያው ንጉሤ ከብራስልስ ዝርዝሩን ልኮልናል።

ገበያው ንጉሤ

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ