ከምርጫው ማግስት ቀጣይ ተግዳሮቶች
ረቡዕ፣ ሰኔ 16 2013ማስታወቂያ
ከኢትዮጵያው ስድስተኛው ብሔራዊ ምርጫ ማግስት የሚመሰረተው መንግሥት ለፖለቲካ ድርድሮች እና የሽግግር ፍትህ እራሱን ቢያዘጋጅ ምርጫው ለአገሪቱ እመርታዊ ውጤት ሊያመጣ እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች ገለጡ። አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ ያጋሩት ሊዕቃኑ በብርቱ ፈተናዎች መካከል ሆኖ የተካሄደው ስድስተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ፍጹማዊነት የተስተዋለበት ባይሆን እንኳ፤ ምርጫውን ተከትሎ የሚመሰረተው መንግሥት ለውይይትና ድርድር እራሱን ካዘጋበት አመርቂ ፖለቲካዊ ውጤት ሊያመጣ የሚችልበት ዕድል አለው ሲሉም አስተያየታቸውን አክለዋል።
ሥዩም ጌቱ
ሸዋዬ ለገሠ
ኂሩት መለሰ