ኤልሳቤጥ ከበደ በመታወቂያ ዋስ ከእስር ተፈታለች
ዓርብ፣ ሚያዝያ 30 2012ማስታወቂያ
ከኮቪድ 19 ጋር በተያያዘ ሀሰተኛ መረጃ በማህበራዊ ሚድያ አሰራጭታለች በሚል አዲስ አበባ በቁጥጥር ስር ውላ ከአንድ ወር በላይ በሐረር ከተማ በእስር ላይ የቆየችው ኤልሳቤጥ ከበደ ትናንት በመታወቂያ ዋስ ከእስር ተፈታለች ፡፡ኤልሳቤጥ ለDW በስልክ በሰጠችው ምላሽ ቆይታዋም ሆነ የፍርድ ሂደቱ ህገመንግስታዊ ድንጋጌን የጠበቀ አልነበረም ብላለች፡፡የክልሉ ፍርድ ቤት ጉዳዯን ማየት እንደማይችል እና ነዋሪነቷ አዲስ አበባ ሆኖ ሳለ ወደ ሐረር መወሰዷ አግባብ አለመሆኑን ስትቃወም እንደነበር ገልፃ በመጨረሻ ክርክሩ ምላሽ አግኝቶ ክሷ ወደ አዲስ አበባ እንዲዞር መደረጉን ተናግራላች፡፡ትናንት ወደ አዲስ አበባ ተወስዳ በመታወቂያ ዋስትና የተለቀቀችው ኤልሳቤጥ በፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የተወሰደው እርምት ተገቢ መሆኑን ጠቁማለች፡፡
መሳይ ተክሉ
ታምራት ዲንሳ
ሸዋዬ ለገሠ