«ኢትዮጵያውያን ከምንጊዜውም በላይ አንድነታቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው »
ማክሰኞ፣ ኅዳር 15 2013ማስታወቂያ
ኢትዮጵያዉያን አንድነታቸዉን ማጠናከር እንዳለባቸዉ በኢትዮጵያ የቀድሞዉ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ዴቪድ ሺን መከሩ።አምባሳደር ሺን ከዶቸ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያዉያን የሐገሪቱን አንድነት ከሚያናጉ ድርጊቶች በመቆጠብ አጠቃላይ ሠላም ለማስፈን መጣር እንዳለባቸዉ አስገንዝበዋልም።ትግራይ ዉስጥ የሚደረገዉ ጦርነት «ከባድ» ዉጪያዊና ዉስጣዊ ተፅዕኖ ሊያስከትል ይችላል የሚል ሥጋት እንዳላቸዉ አምባሳደሩ አልሸሸጉም።
ታሪኩ ኃይሉ
ታምራት ዲንሳ
ማንተጋፍቶት ስለሺ