1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አትሌት ገንዘቤ በዶሃ የዓለም ሻንፒዮና አትሳተፍም

ሐሙስ፣ መስከረም 8 2012

የ1500 ሜትር የዓለም ሪኮርድ ባለቤት አትሌት ገንዘቤ ዲባባ እግሯ ላይ በደረሰዉ ጉዳት ምክንያት በሚቀጥለዉ ሳምንት ዶሃ ካታር ላይ በሚጀምረዉ የዓለም ሻንፒዮና እንደማትሳተፍ የስራ አስክያጅዋ ዛሬ ገለፁ።

https://p.dw.com/p/3PuOW
China Beijing 2015 IAAF Weltmeisterschaft Genzebe Dibaba
ምስል picture-alliance/dpa/S. Suki

የ1500 ሜትር የዓለም ሪኮርድ ባለቤት አትሌት ገንዘቤ ዲባባ እግሯ ላይ በደረሰዉ ጉዳት ምክንያት በሚቀጥለዉ ሳምንት ዶሃ ካታር ላይ በሚጀምረዉ የዓለም ሻንፒዮና እንደማትሳተፍ የስራ አስክያጅዋ ዛሬ ገለፁ። በጎርጎረሳዉያኑ 2015 ቤጂንግ ላይ የ1500 ሜትር ሩጫ ክብር ወሰንን የያዘችዉ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ባለፈዉ ነሐሴ ዙሪክ ስዊዘርላንድ ላይ ከነበረዉ ዉድድር በኋላ በቀኝ ግርዋ ላይ ትንሽ የጉዳት ምልክት እንደታየ ሮይተርስ የዜና ወኪል የአትሌትዋን ስራ አስኪያጅ ጠቅሶ ዛሬ ዘግቦአል።

አዜብ ታደሰ

ኂሩት መለሰ