አርሲ ዞን ወደ መረጋጋት ተመልሳለች
ሰኞ፣ ሰኔ 29 2012ማስታወቂያ
በኦሮምያ ክልል አርሲ ዞን በተለይም ዝዋይ ዱዳ ወረዳ የሚኖሩ ወደ ሠላሳ የሚሆኑ አባወራዎች በወረዳዉ ፖሊስ ጣብያ ተጠልለዉ እንደሚገኙ አሳወቁ። ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸዉ የወረዳዉ ነዋሪዎች ፤ አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ መገደሉ ከተሰማ በኋላ ሃዘናቸዉን ለመግለጽ ወጡ የተባሉ ወጣቶች መሃል የነበሩ ሰዎች ግድያ መፈጸማቸውና ንብረትም ማውደማቸውን ተናግረዋል። የአርሲ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አልዩ በዞኑ ከ 30 በላይ ሰዎች መገደላቸዉን እና ንብረት መዉደሙን ለዶቼቬለ ተናግረዋል ። ይሁንና በአሁኑ ወቅት በዞኑ ሰላም ሰፍኖአል ፤ ተፈናቃዮችም እየተመለሱ ነዉ ብለዋል።
አዜብ ታደሰ
ታምራት ዲንሳ