1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ነዋሪዎችን ያፈናቀለው የአዋሽ ወንዝ ሙላት

ማክሰኞ፣ ጳጉሜን 2 2013

የአዋሽ ወንዝ ሙላት ከ 2400 መቶ በላይ ሄክታር መሬት እርሻ ላይ ጉዳት አድርሶአል፤ በጎርፉ 1495 አባወራዎች አፈናቀለ። አዋሽ ወንዝ በየዓመቱ ጉዳት እንደሚያደርሰዉ ሁሉ ዘንድሮም የገበሪዎችን እርሻ ማሳን አዉድሟል።

https://p.dw.com/p/3zyne
Äthiopien Addis Abeba | Überschwemmungen durch heftige Regenfälle
ምስል Seyoum Getu/DW

በወንዙ ሙላት ጉዳቱ በሦስት ዞኖች በሚገኙ አራት ወረዳዎች ዉስጥ ነዉ

በየዓመቱ ከላይኛው ተፋሰሱ እስከ ታችኛው የአፋር ምድር ከባድ ጎርፍ በማስከተል ነዋሪዎችን የሚያፈናቅለው የአዋሽ ወንዝ ሙላት ዘንድሮም በላይኛው የወንዙ ተፋሰስ ብቻ ከ 1400 በላይ አባወራዎችን ማፈናቀሉ ተገለፀ።

በወንዙ ሙላት ጉዳት የደረሰባቸው በሦስት ዞኖች የሚገኙ አራት ወረዳዎች ናቸውም ነው የተባለው።

አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡት ነዋሪዎች እንደሚሉት ሁሌም በአዋሽ ወንዝ ሙላት ለጉዳት የሚዳረጉት ገበሪዎች ዘንድሮም የእርሻ ማሳቸው ወድሟል ከቤት ንብረታቸውም ተፈናቅለዋል።

Äthiopien Addis Abeba | Überschwemmungen durch heftige Regenfälle
ምስል Seyoum Getu/DW

አዋሽ የተለመደው ጉዳት እንዳያደርስ ቅድመ ጥንቃቄ መደረጉን የገለጸው የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የታሰበው ስራ አስቀድሞ በጣለ ዝናብ ባለመጠናቀቁ ዘንድሮም የወንዙ ሙላት ከ2 ሺህ 400 መቶ በላይ ሄክታር መሬት ሸፍኖ 1 ሺህ 495 አባወራዎችን አፈናቅሏል ብሏል፡፡

ሥዩም ጌቱ

አዜብ ታደሰ

ነጋሽ መሐመድ