1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ትግራይ፤ ለተፈናቃዮች የገቢ ማሰባሰብያ 

ሰኞ፣ ጥቅምት 5 2011

የትግራይ ክልል መንግስት ተፈናቃይ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም ገቢ ማሰባሰብያ መርሃ ግብር ማካሄድ ጀመረ፡፡ በመክፈቻዉ የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ጨምሮ በርከት ያሉ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሐላፊዎችና፣ ባለሃብቶች፣ የተፈናቃይ ዜጎች ተወካዮችና ሌሎች ተገኝተዋል፡፡ 

https://p.dw.com/p/36aQ2
Äthiopien Bezirksregierung in Tigray
ምስል DW/M. Haileselassie

ከ19 ሺህ በላይ ቤተሰብ መሪዎች ግራይ ክልል መጥተዋል

የክልሉ መንግስት በፖለቲካዊ አለመረጋጋት ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች ለማገዝ መዘጋጀቱ ምክትል ርእሰ መስተዳድሩ ዶክተር ደብረፅዮን ገልፀዋል፡፡ እንደ ክልሉ ሰራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፃ ባለፉት ሶስት ዓመታት በሀገሪቱ በነበረው አለመረጋጋት ምክንያት ከ19 ሺህ በላይ ቤተሰብ መሪዎች ተፈናቅለው ወደ ትግራይ ክልል መጥተዋል፡፡ እነዚህ ዜጎች ለማገዝ 1 ነጥብ 5 ቢልዮን ብር ለማሰባሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ የትግራይ ክልል ሰራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገልፅዋል፡፡ 

Äthiopien Bezirksregierung in Tigray
ምስል DW/M. Haileselassie


ሚሊዮን ኃይለስላሴ
አዜብ ታደሰ
ሸዋዬ ለገሠ