1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 ተፈናቃዮቹ ተመለሱ

ዓርብ፣ ሐምሌ 26 2011

ካለፈዉ ሐምሌ 11 ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት ዞኑን ያወከዉን ግጭትና ግድያን ሸሽተዉ በተለይ ሁላ ከተባለዉ ወረዳ ተፈናቅለዉ ምሥራቅ ጉጂ ዞን ሰፍረዉ የነበሩ ከ900 በላይ ነዋሪዎች ወየቀያቸዉ ተመልሰዋል።

https://p.dw.com/p/3NFoD
Äthiopien Stadtansicht Awassa
ምስል DW/S. Wegayehu

ከሲዳማ ዞን ከአንድ ወረዳ የተፈናቀሉ ተመለሱ

ሲዳማ ዞን ለክልልነት «ዘር ቆሌ» የገደለችዉን ቀብራ፣ ያቆሰለችዉን አስታማ አሁን ደግሞ ተፈናቃዮችዋን ወደየቤት ቀያቸዉ ለመለስ አንድ-ሁለት እያለች ነዉ። ካለፈዉ ሐምሌ 11 ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት ዞኑን ያወከዉን ግጭትና ግድያን ሸሽተዉ በተለይ ሁላ ከተባለዉ ወረዳ ተፈናቅለዉ ምስራቅ ጉጂ ዞን ሰፍረዉ የነበሩ ከ900 በላይ ነዋሪዎች ወየቀያቸዉ ተመልሰዋል። የወረዳዉ ባለስልጣናት እንዳሉት ለተመላሾቹ የዕለት ደራሽ ርዳታ ተሰጥቷቸዋልም። ይሁንና የአብዛኞቹ ተመላሾች ከብቶች፤ እና ሌሎች  ሐብት ንብረቶች በመዘረፉና ቤቶቻቸዉ በመጋየቱ መልሶ መቋቋሙ ከባድ እንደሚሆንባቸዉ ተመላሾቹ እየተናገሩ ነዉ።

 ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ