1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ባልደራስ በፓሪስ

ዓርብ፣ ነሐሴ 10 2011

የባልደራስ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኤርሚያስ ለገሠ የተገኙበትን ስብሰባ ያዘጋጁት ፣በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ (ኮምኒቲ) ለዝግጅቱ ሊተባበረን ፈቃደኛ አልሆነም ሲሉ ወቀሱ። የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ (ኮምዩኒቲ) በበኩሉ ስብሰባዉ እንደሚደረግም ሆነ አቶ ኤርሚያስ እንደሚመጡ አስቀድሞ እንዳልተነገረው፣ የአዘጋጆቹ ማንነት እንዳልተገለጸለትም አስታዉቋል።

https://p.dw.com/p/3O0ru
Frankreich Treffen "Addis Abeba Care taker"
ምስል DW/H. Tiruneh

ባልደራስ በፓሪስ

  የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት ወይም ባልደራስ የተባለዉ ስብስብ  ፓሪስ-ፈረንሳይ ዉስጥ በጠራዉ ስብሰባ ሰበብ ፈረንሳይ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን እየተወዛገቡ ነዉ።የባልደራስ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኤርሚያስ ለገሠ የተገኙበትን ትናንት የተደረገዉን ስብሰባ ያዘጋጁት  ወገኖች በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ (ኮምኒቲ) ለዝግጅቱ ሊተባበረን ፈቃደኛ አልሆነም ሲሉ ወቀሱ። የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ (ኮምዩኒቲ) በበኩሉ ስብሰባዉ እንደሚደረግም ሆነ አቶ ኤርሚያስ እንደሚመጡ አስቀድሞ እንዳልተነገረው፣ የአዘጋጆቹ ማንነት እንዳልተገለጸለትም አስታዉቋል። በፓሪሱ የውይይት መድረክ  ላይ የተገኙት አቶ ኤርሚያስ የአዲስ አበባ ህልውና እና ባለቤት ጉዳይ አደጋ ላይ ነው ማለታቸውን የፓሪስዋ ወኪላችን ሃይማኖት ጥሩነህ ዘግባለች።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ