በፓሪስ የኢትዮጵያዉያን ገና በዓል አከባበር
ሰኞ፣ ታኅሣሥ 29 2011ማስታወቂያ
ማኅበሩ በዋንኛነት በኢትዮጵያና በፈረንሳይ መካከል የባህል፤ የትምህርት እና የንግድ ትስስርን ለማጠናከር እንደድልድይ በመሆን የሁለቱን ሃገራት ትስስር ማጠናከር ብሎም ኢትዮጵያዊ ማንነትን ባህልን እና ታሪክን መፈለግን ዋናዉ ትኩረቱ ያደረገ ነዉ። ማኅበሩ የዘንድሮዉን የኢትዮጵያን የገና በዓል ባሳለፉት ወራቶች ያደረጋቸዉን እንቅስቃሴዎች እና የፈረንሳይና የኢትዮጵያን የባህል ልዉዉጥን ለማጠናከር በሚል በፈረንሳይ ነዋሪ ከሆኑ ኢትዮጵያዉያን እና ፈረንሳውያን ጋር በድምቀት አክብሮአል። ትናንት በገና በዓል ዋዜማ «ኢትዮጵያ ፈረንሳይ» ማኅበር መጠለያ ለሌላቸዉ በፓሪስ ጎዳናዎች ላይ ለሚገኙ ስደተኞች የእራት ግብዣም አድርገዋል። በዝግጅቱ ላይ የተገኘችዉ የፓሪስዋ ወኪላችን ዝርዝር ዘገባዉን አዘጋጅታለች።
ሃይማኖት ጥሩነህ
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ