በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የቀረበው ጥሪ
ዓርብ፣ ነሐሴ 7 2013ማስታወቂያ
የኢትዮጵያን ሕልውና ለመታደግ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያ በአንድነት እንዲቆሙ ጥሪ ቀረበ። «በሀገር ጉዳይ ዳር መቆም የለም» በሚል መርሕ ትናንት በተካሄደ ውይይት ላይ ሀገር የማዳን ጥረቱን አቀናጅቶ ማካሄድ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል። በሌላ በኩል በሰሜን ኢትዮጵያ የሚካሄደው ውጊያ ወደ ዐማራና አፋር ክልሎች ተፋፍሞ በቀጠለበት ሁኔታ የአሜሪካ የአፍሪቃ ቀንድ ልዮ መልዕክተኛ ጄፍሪ ፌልትማን ዳግመኛ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚጓዙ ተገልጿል።
ታሪኩ ኃይሉ
ሸዋዬ ለገሠ
ማንተጋፍቶት ስለሺ