በኢንጅነር ስመኘው ሞት ሃዘንና ቁጣዉ እንደቀጠለ ነዉ
ዓርብ፣ ሐምሌ 20 2010ማስታወቂያ
ፖሊስ ሃሙስ ሐምሌ 19 ፤ 2010 ዓ,ም በሰጠው መግለጫ በጥይት ተመተው መሞታቸውን አረጋግጦአል። ኢንጅነር ስመኘው ከጠዋቱ 2 ሰዓት ከ20 አካባቢ መስቀል አደባባይ ከዋናው መንገድ ገባ ብሎ በሚገኘው ቦታ ይዘውት በነበረው ቪ 8 መኪና ውስጥ በመሪው መቀመጫ ሞተው መገኘታቸውን ነዉ የገለፀዉ። በኢንጅነር ስመኘው ሞት የኢትዮዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር፤ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት፤ የኢህአዴግ ምክር ቤት የክልል መንግሥታት እና ሌሎችም ተቋማት የሀዘን መግለጫዎችን አውጥተዋል። ዛሬም የኢንጂኔሩ ሞት ከፍተኛ መነጋገርያ ሆኖ ነዉ የዋለዉ፤ የፊታችን እሁድ ሐምሌ 22 የቀብር ስነስርዓታቸዉ እንደሚፈፀም ተመልክቶአል። በኢንጂኔሩ ሞት ያለዉን ሁኔታ የአዲስ አበባዉን ወኪላችንን በስልክ ጠይቀነዉ ነበር።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ