በአፋር ክልል ግጭት 10 ሰዎች ተገደሉ
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 17 2011ማስታወቂያ
ላለፉት ሦስት ቀናት በዘለቀው ግጭት የሟቾች ቁጥር ከ20 በላይ እንደሚዘልል፤ ተመሳሳይ ቁጥር ያላቸው ወገኖች ደግሞ ቆስለው ህክምና ላይ መሆናቸውም ተነግሯል። የክልሉ ነዋሪዎች በአካባቢው ተደጋጋሚ ጥቃት ቢደርስም የመከላከያ ሠራዊት ተገቢ ያሉትን ጥበቃ አላደረገልንም ሲሉም አመልክተዋል። የሀገር የመከላከያ ሚኒስቴር የሚዲያዎች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በበኩሉ ስለጉዳዩ መረጃ የለኝም ብሏል። ከአዲስ አበባ ዮሐንስ ገብረ እግዚአባሔር ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአባሔር
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋኅ መሐመድ