1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአገራዊ ጉዳዮች ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት 

ሐሙስ፣ ጥቅምት 5 2013

በሕገ መንግሥት እና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በፓርቲዎች አደረጃጀትና ችግሮቻቸው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ቅራኔዎች እንዲሁም ነፃና ትክክለኛ ምርጫ እንዴት ማካሔድ ይቻላል በሚሉ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ተወያይተዋል።በውይይቱ አገራዊ መግባባት መፍጠርና ሕዝብ ሊጠቀም በሚችልባቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ እንዲደረስ ተጠይቋል።

https://p.dw.com/p/3jzRt
Äthiopien Addis Ababa Forum der politischen Parteien
ምስል Solomon Muche/DW

በአገራዊ ጉዳዮች ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውይይት 

በፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የታቀፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሕገ መንግሥት እና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በፓርቲዎች አደረጃጀትና ችግሮቻቸው፣ ኢትዮጵያ ውጥ በሚስተዋሉ የፖለቲካ ቅራኔዎች እንዲሁም ነፃ እና ትክክለኛ ምርጫ እንዴት ማካሔድ ይቻላል በሚሉ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ አገራዊ መግባባት መፍጠርና አገርን እየጎተተ ያለን ሽኩቻን በማስወገድ ሕዝብ ሊጠቀም በሚችልባቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ እንዲደረስ ተጠይቋል። በውይይቱ መክፈቻ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተገኝተዋል። 

ሰሎሞን ሙጬ


ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ