1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአክሱም ሰብዓዊ ቀዉስ ጉዳይ የኢሰመኮ የመጀመርያ ዘገባ

ረቡዕ፣ መጋቢት 15 2013

በአክሱም ከተማ በኤርትራ ወታደሮች ዉስን በሆነ መልኩ በኢትዮጵያ ወታደሮች ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን ማረጋገጡን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ገለፀ።

https://p.dw.com/p/3r3S7
Äthiopien Daniel Bekele
ምስል DW/S. Muchie

45 የተጎጂ ቤተሰቦችን፣ የዓይን ምስክሮችንና የሃይማኖት መሪዎችን በማነጋገር ተረጋግጦአል

 

በአክሱም ከተማ በኤርትራ ወታደሮች ዉስን በሆነ መልኩ በኢትዮጵያ ወታደሮች ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን ማረጋገጡን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ገለፀ። ኮሚሽኑ ባወጣዉ የመጀመርያ ደረጃ ሪፖርት እና ለዶቼ ቬለ በሰጠዉ ተጨማሪ ማብራርያ ሲቪል ዜጎች ተገድለዋል፤  የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ በንብረት ላይ ከፍተኛ ያለዉ ጉዳት ደርሶአል፤ ብሎአል። 
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ትግራይ ክልል ደረሰ ያለውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና በሲቪሎች ላይ የተፈጸመውን ጥቃት አስመልክቶ የመጀመሪያ ደረጃ (ቀዳሚ) ሪፖርቱን ይፋ አድርጎአል። ኢሰመኮ  ዘገባው፦ «ትግራይ ክልል፤ በአክሱም ከተማ የተፈጸመው ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በአጠቃላይ በክልሉ የተሟላ ምርመራ የማድረግን አስፈላጊነት   ያመለክታል» ብሏል።

 

ዮሃንስ ገብረግዚአብሔር

አዜብ ታደሰ

ነጋሽ መሐመድ