1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአማራ ክልል የተፈናቃዮች ይዞታ

ሐሙስ፣ ጥቅምት 25 2014

በክልሉ ህወሓት በያዛቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች በህመምና እና በምግብ እጦት፣ ቡድኖ ወርሮ በለቀቀው የሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ ደግሞ የህክምና ቁሳቁሶችና መድኃኒቶች በመዘረፋቸው፣ ከ100 በላይ ሰዎች መሞታቸውን የአማራ ክልል መንግሥት አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/42aYh
Bahir Dar | Binnenflüchtlinge aus Waghemra
ምስል Alemnew Mekonnen/DW

«በመድኃኒት እና ምግብ እጦት የሞቱ አሉ»

 

በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖች ከምግብ እና ህክምና እጦት ጋር በተያያዘ ለከፋ ችግር መዳረጋቸው እየተነገረ ነው። በክልሉ ህወሓት በያዛቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች በህመምና እና በምግብ እጦት፣ ቡድኖ ወርሮ በለቀቀው የሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ ደግሞ የህክምና ቁሳቁሶችና መድኃኒቶች በመዘረፋቸው፣ ከ100 በላይ ሰዎች መሞታቸውን የአማራ ክልል መንግሥት አስታውቋል። የክልሉ የአደጋ መከላከል፤ ምግብ ዋስትና እና ልዩ ድጋሚ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ጉዳዩን የተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል።

ዓለምነው መኮንን 

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ