1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በትግራይ ጉዳይ የአዉሮጳ ኅብረት አስተያየት  

ዓርብ፣ ሰኔ 4 2013

የአዉሮጳ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርዙላ ፎንደርላይን በኢትዮጵያ በተለይም ትግራይ ክልል የሚታየዉ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ነዉ። በመሆኑም ሁኔታዉን ለመረዳት ባለድርሻ አካላት እንዲረዱት ለማድረግ ጥሪ ማድረግ አስፈላጊ ነዉ። በትግራይ ያለዉ ሁኔታ እጅግ አስከፊ ነዉ የባሰ ነገር እንዳይፈጠር ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል።

https://p.dw.com/p/3ulb3
EU-Parlament Sitzung am 9.6.2021
ምስል Julien Warnand/EPA Pool/AP/picture-alliance/dpa

በትግራይ ነገሩ እንዳይባባስ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል

የአዉሮጳ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርዙላ ፎንደርላይን በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሚታየዉ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ በመሆኑ ትኩረት መደረግ አለበት ሲሉ ተናገሩ።  ባለድርሻ አካላት በትግራይ ያለዉ ሁኔታ እንዲያዉቁት ለማድረግ ጥሪ ማድረግ ያለብን አሁን ነዉ ብለዋል። ፎንደርላይን ይህን የተናገሩት የበለፀጉት ሃገራት G7 ጉባዔ ላይ ለመገኘት ወደ ኮርንዎል ብሪታንያ ከመጓዛቸው በፊት ነዉ።  የኅብረቱ ካዉንስል ፕሬዚደንት ቻርልስ ሚሼልም አብረዋቸዉ ተጉዘዋል። የብረስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ አጠናክሮ ልኮልናል።    

ገበያዉ ንጉሴ

አዜብ ታደሰ