በተገቢው መንገድ ሥራቸውን የማያከናውኑ የትምህርት ተቋማት
ሐሙስ፣ ነሐሴ 16 2011ማስታወቂያ
ኤጀንሲው በዚህ ሕገወጥ እና የማይጠበቅ ሥራ ተሰማሩ ያላቸው ባሕር ዳር ፣ ጅማ ፣ ሀረማያ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች የተቋማቱን ሃብትና መምህራን በመጠቀም ከሌሎች ተቋማት ጋር በመሆን ተገቢነት የጎደለው ሥራ ላይ ተሰማርተው መቆየታቸውን ፣ አሁን ግን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን ክልከላ ተከትሎ 3ቱ ከድርጊታቸው
የተቆጠቡ ሲሆን ጅማ ዩኑቨርሲቲ ግን የሚኒስቴሩን አቅጣጫ ወደጎን በማለት አሁንም አስተምራለሁ እያለ ተማሪዎችንም እየመዘገበ እንደሚገኝ ኤጀንሲው ዛሬ አዲስ አበባ ላይ በሰጠው መግለጫ አመልክቷል። ዩኒቨርሲቲዎቹ መንግሥት የማያውቃቸውን ተማሪዎች እያስተማሩ ከፍተኛ ገንዘብ እየሰበሰቡ ነው የሚለው ኤጀንሲው በተለይ ጅማ ዩኑቨርሲቲ የሚያስከፍለው ገንዘብ የተጋነነና አዲስ አበባ ላይ አብሮት እየሠራ ያለውንም ተቋም እውቅና የተሰጠው ባለመሆኑ ተገቢው እርምጃ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በኩል እንዲወሰድበት ተይቋል። በእነዚህ ተቋማት የተመረቁም ይሁን እየተማሩ ያሉት ተማሪዎች እጣን በተመለከተ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ ወደፊት እርምጃ እንደሚወሰድና ግልጽም እንደሚደረግ ተገልጿል። ከአዲስ አበባ ሰሎሞን ሙጬ ዝርዝር ዘገባ አለው።
ሰሎሞን ሙጬ
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ